- በሊቢያ፣ በየመን እና በሌሎችም ክርስቲያኖች ለጥቃት በተጋለጡባቸውና የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ በሚገኙባቸው አገሮች ከተጨማሪ ጉዳት ለመታደግ የሚሠራ ኮሚቴ ተቋቁሟል
- በአዲስ አበባ እና በአህጉረ ስብከት የሰማዕታት ቤተ ሰዎችን እያፈላለጉ የማጽናናት እና የመደገፍ መርሐ ግብር ይካሔዳል
- ከሊቢያው የግፍ ተግባር ጋራ በተያያዘ ባሉ ኹኔታዎች ላይ በየዕለቱ እየተሰበሰበ በመምከር መልእክት ለማስተላለፍ የወሰነው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬም መግለጫ ይሰጣል
[…] Source:: haratewahido […]
ኀዘኑን ለማዘን ሰብዓዊነት በቂ ነው፡፡ኀዘኑን በቅጡና በተቋማዊ መንገድ፣ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን ተላብሶ መወጣት ግን ብልኅነትንና ቅንነትን ሳይጠይቅ አይቀርም፡፡
አንዳንድ ወንድሞቻችን ቅ/ሲኖዶሱ ገና መግለጫ ሳይሰጥ “ይሄ ጉደኛ ሲኖዶስ ምን ሊል ይኾን?” በሚል ፍረጃ ሲያሟሙቁ ቆይተው፡-(1)መንግሥት እንኳ ለራሱ በተደናበረበት ሰዓት አባቶች በመንበረ – ፓትርያርክ የሰጡትን መግለጫ እየበለቱ ራስን ማጽደቅን፣(2)አስቀድሞ ገና አባት የለንም እያሉ ማሳቀልን፣(3)ብፁዐን ጳጳሳት አባትነታቸው ቢካድ እንኳ ኢትዮጵያዊ የዜግነት ተቆርቋሪነት የሌላቸው ይመስል ስለ ሰቆቃው አንዳች እንዳልተሰማቸው ማስመሰልን፣(4)በተለመደው የግብፅ ኮፕቲክ ሚዛን አባቶችን ለክቶ መቁረጥን ተያይዘውታል፡፡ነውር–ርኵሰት–ጥፋት ነው፡፡
መጀመሪያ ዘመነ – ሰማዕታት ለኢኦተቤክ እንግዳ አይደለም፡፡ወደ ኢየሩሳሌም ሲደረጉ በነበሩ የሲና በረሃ መንፈሳዊ ጉዞዎች፣በኢየሩሳሌም የመስቀል ጦርነት ወቅትና እሱን ተከትሎ በነበረው ጊዜ በኢየሩሳሌም በነበሩ መነኮሳት፣በዮዲት፣በግራኝ፣በሱስንዮስ፣በመካከለኛው ዘመን ሰሎሞናዊ ነገሥታት፣በደርቡሽ፣በጣሊያን፣በደርግ፣በዘመነ – ኢህአዴግም በአክራሪ እስልምና በ1984/5 ዓ.ም እና በ1998/9 ዓ.ም የበዙ ውሉደ – ጥምቀት ስለ ፀናች ሃይማኖት ተሰይፈዋል፡፡እሱን ኀዘንና የሰማዕታቱን ምስክርነት የኢኦተቤክ በተግባርም በጽሑፍም ወደ ቋሚ ምስክርነት ስትቀይር ኖራለች፡፡ትኖራለች፡፡
ስለዚህ አሁንም አጓጉል የግብፅ ሚዛንን ከፍ አድርጎ የራስን አባትና ተቋም ከማሳነስ ጎዳናችን ተመልሰን አባቶች የሚነግሩንን በጽሞና እየተከታተልን በአባትና ልጅ ሥርዓት መሄድ የቀናው ጎዳና ነው፡፡እናንተ ወንድሞቻችን(የሐራ ብሎግ አስተዳዳሪዎች) በዚህ ረገድ እያደረጋችሁት ያለው የቤ/ክ ድምጽ የመኾንና ኀዘኑን ላልተገባ አጀንዳ ማጀቢያ ማድረግን ሳይኾን ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊነትንና ለኦርቶዶክሳዊነት የተከፈለን ዋጋ ከነ ክርስቲያናዊ ክብሩ፣አሸኛኘቱ፣ዝክሩ፣ቅ/ሲኖዶሳዊ ብያኔው…ለማቅረብ የጀመራችሁት መንገድ የጽድቅ መንገድ ነው፡፡ደስ ያሰኛል፡፡
የሰማዕታቱ በረከት ይሕን በምታቀርቡ በእናንተ፣በምናነበው በኛ እንዲያድር አምላከ – ቅዱሳን ይርዳን፡፡ኀዘኑን የኀዘን ዳርቻ ያድርግልን፡፡አሜን፡፡