(ሪፖርተር፤ ኅዳር ፳፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)
ኄኖክ ያሬድ
የኢትዮጵያው የመስቀል ክብረ በዓል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ዩኔስኮ አስታወቀ፡፡ ዩኔስኮ የመስቀል ክብረ በዓልን (Commemoration feast of the finding of the True Holy Cross of Christ) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ኅዳር 25 ቀን ይፋ ያደረገው፣ በኢንታንጀብል (መንፈሳዊ) ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃና ክብካቤ ላይ የሚሠራው ኮሚቴው ስምንተኛውን ጉባኤ እያካሄደባት ካለው የአዘርባጃኗ ባኩ ከተማ ነው፡፡
ስለ ቅርሱ የመረመረው ኮሚቴ ባቀረበው ውሳኔ ሐሳብ ላይ እንደተመለከተው፣የመስቀል ክብረ በዓል የኢትዮጵያን ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊቶችን የያዘ፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ መምጣቱና በአገሪቱ ማኅበራዊ አንድነትንና የርስ በርስ ትስስርን፣ ብዝኃነትንም የሚያንጸባርቅ፣ በበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች መካከል ትስስርን የፈጠረ በመኾኑ ዓለም አቀፍ መስፈርቱን አሟልቷል ብሎታል፡፡
የዩኔስኮ ኮሚቴው በረቡዕ ስብሰባ ውሎው ከመስቀል ሌላ ከተለያዩ አገሮች 13 መንፈሳዊ ባህላዊ ቅርሶችን በሰው ዘር ቅርስነት መመዝገቡንም በድረ ገጹ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ መስቀልን ጨምሮ እ.ኤ.አ. በ2013 የተመረጡትን የ14ቱ መንፈሳዊ ባህላዊ ቅርሶች ገጽታ የሚያሳዩ ቪዲዮዎችና ፎቶዎችም በዕለቱ በድረ ገጹ ላይ መለቀቃቸው ታውቋል፡፡
በየዓመቱ መስከረም 17 ቀን በመላ አገሪቱ በአደባባይ ደመራ የሚከበረው የመስቀል ክብረ በዓል የመጀመርያው መንፈሳዊ (ኢንታንጅብል) ባህላዊ ቅርስ ኾኖ በዩኔስኮ የተመዘገበላት ኢትዮጵያ፣ ዘጠኝ ግዙፍ (ታንጀብል) ቅርሶች ማስመዝገቧ ይታወቃል፡፡
Egiziabher yemasgen Melkam zenanaw!!!
wonderful.This is the result of the good effort of His holiness Abune Paulos and our smart government. may the Almighty God rests in good place the soul of our beloved Patriarch Abune Paulos and He may bless our leaders.
LeMeskel Beal kibirr – Siyansew new. Lefetari sira gin – yihem aydenkim. yeErsu wileta yeErsu deginet hulem dinkk newina. “Beliwo leEgziAbHer Girum Gibrike.” Dinkk zena new lebetekirstianachin.
Thanks to God ! We all Ethiipian have to celebrate this special day.
enkuan des alen
Gena sintu yaltemezegebe ale!!!
egziabhir ytemesgen yehun
konjo zena