ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በመጀመሪያው ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባው ስለሚያተኩርባቸው ጉዳዮች ዛሬ፣ ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ጥዋት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርኩ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በቅዱስነታቸው መግለጫ መሠረት ምልአተ ጉባኤው÷ ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት ምእመናንን ስለ መጠበቅና ማብዛት፣ የቤተ ክርስቲያንን የትምህርት ተቋሞች በጥራትና አደረጃጀት በመለወጥ ከመማርና መሠልጠን አልፎ መከራን ለመቀበል የተዘጋጁ ላእካነ ወንጌልን አብቅቶ ስለማውጣት፣ ፍጹም የዕድገት ለውጥ ለማምጣት ስለሚያስችለው የፋይናንስና የመልካም አስተዳደር ጅምር ጥናት ሂደት፣ በቅዱስ ሲኖዶሱ የውሳኔ አሰጣጥ የቤተ ክህነት ልዩ ልዩ ክፍሎች ሓላፊዎች፣ ካህናት፣ ሊቃውንት፣ ወጣቶችና ምእመናን ውክልናና ተሳትፎ ስለሚረጋገጥበትና የቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ ሰፊ ድጋፍና ተቀባይነት ስለሚያገኝበት አሠራር ይመክራል፤ ውሳኔም ያሳልፋል፡፡
‹‹የአክራሪነት፣ አሸባሪነትና ጽንፈኝነት›› ተግባራትን በማውገዝ የክርስቶስ መልእክት የኾነውን ሰላምና እኩልነት፣ መከባበርና መቻቻል፣ አብሮ መልማትና ማደግ ለሕዝቡ በየቀኑ ማስተማርና መስበክ እንደሚገባ የገለጹት ፓትርያርኩ፣ ‹‹የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ችግሮችን በውይይትና በውይይት ብቻ የመፍታት ባህል መደገፍና ማጎልበት አለብን፤›› ሲሉም መክረዋል፡፡
አጀንዳዎቹ÷ በፍትሕ መንፈሳዊ በተደነገገው መሠረት የተሰበሰበው ምልአተ ጉባኤው መንፈስ ቅዱስ በሚገልጽለት መንፈሳዊ ጥበብ እየተመራ መፍትሔ ማግኘት ያለባቸው ጉዳዮች መፍትሔ እንዲያገኙ፣ በጥልቀት፣ በማስተዋልና የሓላፊነት መንፈስ በተላበሰ ወኔ በመወያየት ሊወስንባቸውና ለተግባራዊነታቸው ሊረባረብባቸው እንደሚገባ ምልአተ ጉባኤውን በርእሰ መንበርነት የሚመሩት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በመግለጫቸው አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም ፓትርያርኩ፣ መንፈስ ቅዱሳዊና ሐዋርያዊ ዐቢይ ጉባኤው በስብሰባው መጨረሻ የሚደርስበት ውሳኔና የሚያወጣው መመሪያ በውጤቱ÷ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስፋፋ፣ ማኅበረ ካህናቱንና ማኅበረ ምእመናኑን የሚያስደስት፣ በሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን ተከታዮች ዘንድ በናፍቆት የሚጠበቀውን የለውጥና የዕድገት ጎዳና የሚከፍት እንዲኾን በመግለጽ መግለጫቸውን ደምድመዋል፡፡
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባመክፈቻጋዜጣዊ መግለጫ ዐበይት የትኩረት ነጥቦች
በድንበር የለሽ ስብከተ ወንጌል በርከት ያሉ በጎችን የማርባትና የመጠበቅ ሥራ
- ከትንሹ የሥልጣነ ክህነት ሹም ጀምሮ እስከ ትልቁ የቤተ ክርስቲያን ባለሥልጣን ድረስ ለስብከተ ወንጌል መስፋፋት ተልእኮ በንቃት፣ በሙሉ ዕውቀት፣ በተነሣሽነት፣ በፍጹም ፈቃደኛነት እንዲነሣሣና እንዲሰለፍ የሚጠበቀውን ያህል አልተሠራም፡፡
- ቤተ ክርስቲያን በጥምቀት ወልዳ፣ በሥጋ ወደሙ አሳድጋ፣ ወልደ ማርያም፣ ገብረ ሚካኤል ብላ የሠየመቻቸው ልጆቿ ከጉያዋ እየተነጠቁ ወደ ሌላ ካምፕ ሲወሰዱ እርስዋ የወላድ መሐን የኾነችበት፣ ያልወለዱና ያላሳደጉ ባለብዙ ቤተሰብ የኾኑበት ክሥተት እያጋጠመ ነው፡፡
- የቅዱሳን ሐዋርያት ሥልጣን ወራሾች እንደመኾናችን ቁጥር አንድ ሥራችን በድንበር ሳይገደቡ ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋት ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በሥሩ ያሉትን በጎች መጠበቅ ብቻ ሳይኾን ድንበር የለሽ ትምህርትና ስብከት በማካሄድ ከዛሬ ጀምሮ በየዓመቱ በርከት ያሉ በጎችን የማርባትና የመጠበቅ ሥራ ሊያሠራው የሚችል አሠራር መቀየስ አለበት፡፡
የትምህርት ተቋሞቻችንን በብዛትም በጥራትም በአደረጃጀትም በመለወጥ ትንሣኤዎቻቸውን ማብሠር፤
- የምንሾማቸው ዲያቆናት፣ ቀሳውስትም ኾኑ ኤጲስ ቆጶሳት በተለምዶ የተሾሙ ሳይኾኑ ጌታችን እንዳደረገው የተማሩ፣ የሠለጠኑ፣ ነገሩ የገባቸውና መከራውን ለመቀበል የተዘጋጁ ሊኾኑ ይገባል፡፡
- የአብነት ት/ቤቶቻችን፣ የካህናት ማሠልጠኛዎቻችንና የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞቻችን በብዛትም በጥራትም በአደረጃጀትም ተማሪውን በትክክል ለመለወጥና ለመቅረጽ በሚያስችል አዲስ አሠራር ማስተካከልና ማብቃት አለብን፡፡
- ቤተ ክርስቲያናችን የሃይማኖት እንከን ሳይኖራት፣ ሞያ ሳያንሳት፣ ተቆርቋሪ ምእመናን እያሏት በአያያዝና በአመራር ምክንያት የምትወቀስበትና ልጆቿን የምታጣበት ታሪክ መገታት አለበት፡፡ ይህን በወሳኝ መልኩ ለማስተካከል የትምህርት ቤቶቻችንን ትንሣኤ የሚያበሥር፣ ዕድገታቸውንና ጥራታቸውን የሚያፋጥን ጠንካራ መሠረት ዛሬ ማስቀመጥ ይኖርበታል፡፡
ስለ ዘመናዊ የፋይናንስ አሠራርና መልካም አስተዳደር የተጀመረው ጥናት ሂደት
- ምእመናን የሚፈለገውን ዐሥራት፣ በኵራትና ቀዳምያት በሕጉ መሠረት እየሰጡ አይደለም፤ የሚሰጡትም ስጦታ በየመንገዱ እየተንጠባጠበ ወፎች የሚለቃቅሙት ይበዛዋል፡፡ የሚፈለገውን ያህል ተደራጅተን፣ መስለን ሳይኾን ኾነን፣ በሁሉም ነገር ተዘጋጅተን ማስተማር፣ ዘመኑ በሚፈቅደው የፋይናንስ ቁጥጥርና አያያዝ መጠቀም አለብን፡፡
- ከወገንተኝነትና አድሏዊነት በአግባቡ ያልተላቀቀው አስተዳደራችን የቤተ ክርስቲያናችንን ተሰሚነት ክፉኛ እየጎዳው ነው፡፡ በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ጉባኤው የማፍረስ ሳይኾን የመገንባት ግብ ያለው ራእይ አንግቦ ሥር ነቀል የኾነ ፍጹም የዕድገት ለውጥ ለማምጣት የሚያስችለውን አሠራር መቀየስ ይገባዋል፡፡
በቅዱስ ሲኖዶስ የውሳኔ አሰጣጥ የካህናትና ምእመናን ተሳትፎ ስለማረጋገጥ
- ቅ/ሲኖዶስ በጉዳዮች ካህናትንና ምእመናንን እያሳተፈና በሐዋርያዊ ሥልጣኑ እያጸደቀ የውሳኔውን ተቀባይነትና ድጋፍ የሚያሰፋበትንና የሚያረጋግጥበትን አሠራር ይተክላል፡፡
ምዕመናን ሁላችን በፀሎት አባቶቻችን ማገዝ አለብን
I can’t see the Amharic full history frome my device but just I Guss it is all about one Orthodox Church in Ethiopia and all over the world where Ethiopians refuges places .this is the big news that I always praying and regretting all the time God may Bless all our church leaders and make theme creat one church like we had before !!God Bless Ethiopia!!!
ቤተክርስቲያኗ ከኛ የምትጠብቀውን ሁሉ ከኛ ለመለገስ ተግተን በጋራ በመስራት ያለፉት 23ዓመታት ዘንድሮን ጨምሮ ማለት ነው በቤተክርስትያኗ ላይ እና በምእመኖቿ ላይ እየደረሰ ያለውን ከባድ መከራ ፣በደል፣ግፍ፣ሰማዕትነት ለማስቆም በሁለመናችን ከአባቶች ጎን መቆም ይኖርብናል አምላክ ይርዳን እናንተን አባት አድርጎ የሰጠን እግዚኣብሄር ይመስገን።
አለሁ እድሜየ ገፍቶአል የማይሉ ናቸው ና እኛ ምዕመናኖቹ ተሰላችተን የምንወዳትን ቤተክረስቲያን ጥለን ከመለየታችን በፊት በህማም ላይ ያሉትን ና እድሜአቸው የገፋውን እግዚአብሄር ረድቶዎት በጡረታ እንዲገለሉ ማድረግ ይጠበቅበዎታል ፡፡ብጹዕ ወቅዱስ አባታችን ስለ ግል ጥቅማቸው ስለ ሥጋ ዘመዶቻቸው ጥቅም ብቻ የቆሙ መንፈስ ቅዱስ ነው የሚመራው በሚባልለት ሲኖዶስ ተሰግስገዋል ሀገረስበከቶቹን እንደግል ሀብታቸውም የሚቆጥሩ አሉ አንዳንዶቹም እድሜአቸው የገፋ በአደረባቸው ህማም ምክንያት ተንቀሳቅሰው የማያገለግሉ ነገር ግን ጡረታ መውጣት ሲገባቸው ያልወጡ በቃኝ ታምሜ
Tkkel New ewnet New beteley ketehadesso yegelaglune Hulachenem Entseleye.
መልካም ጅምር ነው አባቶቻችንን እግዚአብሔር ይርዳቸው
dinber yalesh yewengel agelgelot endiset masebu ejig des yasenyal. entseley.
Abatachn jmarewot melkam now eskemechereshaw yetsenu hunu. Yebetekrstiyanachnn tnsae yasayen,
bemahiberu sim yetesebesebut batekalay lewegn ayhonu lebete kirsitiyan ayhonu terefe ayihud nachehu zendro yleyal seytan besew enjeralay ashiwa yemtbetnu yerasachhun enjera yemtabesilu dibki yepoletika ajenda tegaltal yketlal
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያኑን የመሰረታት በቃሉ ነውና በትምህርትና በትምህርት ቤት ላይ ብዙ መሥራት ያስፈልጋል የሚለውን በጣም ግሩም ነው። የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የሐዋርያት ጉባኤ እንዲሆን እግዚአብሔር ይርዳን።
መልካም ጅምር ነዉ አባቶቻችን እግዚአብሐየር ይርዳቸዉ
kkkkkkkkkkk…..”ቤተ ክርስቲያን በጥምቀት ወልዳ፣ በሥጋ ወደሙ አሳድጋ፣ ወልደ ማርያም፣ ገብረ ሚካኤል ብላ የሠየመቻቸው ልጆቿ ከጉያዋ እየተነጠቁ ወደ ሌላ ካምፕ ሲወሰዱ እርስዋ የወላድ መሐን የኾነችበት፣ ያልወለዱና ያላሳደጉ ባለብዙ ቤተሰብ የኾኑበት ክሥተት እያጋጠመ ነው፡፡”…..በጣም ይገርማል ውሻ ከሄደ ጅብ ይጮሃል ነው ያሉተ….ዛሬ ነው እንዴ የሚታያቹህ ወይስ አለቆቻቹህ የህዝቡን ስሜት በዚህ ውሰዱ ብለዋቹህ ነው……የተባሉት ካምፖች የዛሬ 20 ዓመት ካልነበሩበት ከሌላው ህዝበ እኩል የሚገዳደሩበትን ቁጥር ሲይዙና በትምህርት፤ ፖለቲካውና በኢኮኖሚው ቁልፍ ቦታዎችን ሲይዙና ከውስጥ አርበኞችን ሰግስገው ሁለት እግራቸውን መሬት ላይ ካቆሙ በኋላ ነው የሚነቁት…ወይስ ሌላ ተልዕኮ ለመፈፀም………ለማንኛውም በሀገር ውስጥኛ በውጭ የተማረውንና ለሃይማኖት ክብር ያለውን ውጣት ጥርግ አርገው ግዴለሹን ከተውት በኋላ ከላይ ላይ ብቻ የሚደረግ መፈራገጥ ብዙም ለውጥ ያለው አይመስለኝም ……ለውጡ ከውስጥ መጀመር አለበት የሚል ነው ሃሳቤ
“””diyabilos zenarun cherese kesetun aragefe bête keresetiyanen gin alegodatem”””” yelekes yesedeb AFE YETESETEW DIYABELOS NEW ENA SHIMUTUN TETEN EWONET YE EGZIABEHER SEW KEHONE ENETSELEY KEGNA YEHONU BIWOTU ENKUAN YEMETALU KALEHONU GIN ENEDEWOTU YEKERALU.””””EGZIABEHER TEWAGI NEW SEMUM EGEZIABEHER NEW””””.
ብጹዕ ወቅዱስ አባታችን ስለ ግል ጥቅማቸው ስለ ሥጋ ዘመዶቻቸው ጥቅም ብቻ የቆሙ መንፈስ ቅዱስ ነው የሚመራው በሚባልለት ሲኖዶስ ተሰግስገዋል ሀገረስበከቶቹን እንደግል ሀብታቸውም የሚቆጥሩ አሉ አንዳንዶቹም እድሜአቸው የገፋ በአደረባቸው ህማም ምክንያት ተንቀሳቅሰው የማያገለግሉ ነገር ግን ጡረታ መውጣት ሲገባቸው ያልወጡ በቃኝ ታምሜ አለሁ እድሜየ ገፍቶአል የማይሉ ናቸው ና እኛ ምዕመናኖቹ ተሰላችተን የምንወዳትን ቤተክረስቲያን ጥለን ከመለየታችን በፊት በህማም ላይ ያሉትን ና እድሜአቸው የገፋውን እግዚአብሄር ረድቶዎት በጡረታ እንዲገለሉ ማድረግ ይጠበቅበዎታል፡፡
ጥርግ ያለ ሞኝነታቹሁን ህዝቡ ሲነቃና የመንፈሱ ጥሪን መልስ ሲያገኝ ነው የሚሄደው …ከተቻላቹህ ዘመናዊነት(የዛሬ 100 እና 200 ዓመት ለነበረ ትውልድ የሚነገር ወሬ ይዛችሁ ..እንዴት ይህን ትውልድ ለመያዝ ትሞክራላቹህ……ይህ ህዝብ ፍም እሳት ነው….ነው ያለው) እንዴት አላምዶና ተራ የአባቶችን ተረት እንዴት ቀርፎ እንደሚወጣ ስሩ
These are the most critical issues of discussion,specially now a days, by the Holy Synod upon which we expect persistent decision and enforcement with out anybody’s intervention to bring change and prosperity to our CHURCH. Besides to this, ordination of new bishops has to be seriously considered not to repeat the past history mistake. Let our CHURCH first get relief from those corrupted and racist church leaders who defame the religion. Courage and determination is required in this case. The “Government” he himself must take this as a necessary step to combat corruption.
“የሃይማኖት እንከን የሌለባትና” hahahaha
men letel felek ?ene eko yemigeremegni nechochu enkuan be orthodox emenet eye tegeremu sikenu enanete gin kenesu beworesachihut ewonet meseloachihu setetalelu betam tasazenalachihu!enesus balemawok enanete gin kawokachihut behuwala lekadachihu enazenalen “kemayamen yelek hayemanotun lekade woyolet “yemilewon ayetachihu kehone gizew gena new ena beneseha temelesu.egeziabeher “””ANED GIZE LEKEDUSAN SELE TESETECH HAYEMANOY ENDETEGADELU””””yelal ena asebebet ???Amelakem bemeder lay tenedelako ayedelem kebarenet netsa yawotan Hawareyatem sele keresetos belew mekeran tekebelew new yalefut enji andem hawareya tenedelako yalefe hawareya yelem ena tsom tselot segedet fereteh kewonet ke andua hayemanot wonedeme ehete ebakachihu tedebaleku “”betekeresetiyan hule sele enanete tetseleyalech “”””SELETESEDEDU SEWOCH AND ADEREGEN EYALECH “”””NUUUUUUUUU.
እባካችሁ አሁን የጀመራችሁትን የቤተክርስቲያናችን ታሪክ እና እውነተኛነት እያጠፋ ያለውን ይህን መንግስት በመፍራት ወደኋላ እንዳትሉ፡፡ ስለ እግዚአብሔር ክብር ስትሉ የቤተክርስቲያናችን ህልውና ታደጉልን እግዚአብሔር ይርዳችሁ አሜን፡፡
DIYABELOS ZENARUN CHERESE KESETUN ARAGEFE BETE KERESETIYANEN GIN ALEGODATEM.YELEKES YE MISADEBEBET AFE YETESETEW DIYABELOS NEW ENA SEDEBUN SHIMUTUN TETEN BETSELOT ENEBERETA???”EGZIABEHER TEWAGI NEW SEMUM EGEZIABEHER NEW”DENEGEL ATELEYEN.AME……….
It is a good start.Let us prey with them for the reality of our church dream!
አቤት አቤት እንዴት ነዉ ነገሩ፡ ጂብ ከሄደ ዉሻ ጮኸ እኮ ሆነ ነገሩ፡ ህዝቡ ከሲመቱ በፊት እርቁ ይቅደም እያለ ሲጮህ ሰሚ አጥቶ አሁን ስልጣንን ካመቻቹ በሁዋላ ተቆርቁዋሪ መሆን ምን ይሉታል? የከፋ የሚሆነዉ ደግሞ የዉጮቹን ባቶችን ስም እያጎደፉ እንደፓለቲካ ፓርቲ ራስን ንጹህ አድርጎ መጽሀፍ መጻፍ ምን ይሆን የሚፈይደዉ? ከመወጋገዝ እንደ ሀይማኖቱ መመሪያ በእርቅ መፍታት አይሻልም? አምላከ እስራዔል መረን ባክህ።