- የቅዱስ ሲኖዶሱን የአመራር፣ የአስተዳደር፣ የቁጥጥርና የመወሰን ብቃት ያግዛሉ
- የቅዱስ ሲኖዶሱን አካላት ለማቀናጀትና አሠራራቸው ጥንካሬ እንዲኖረው ያስችላሉ
- ምልዓተ ጉባኤው በአጭር ጊዜ የሚይዛቸው በርካታ አጀንዳዎች የተጠና ውሳኔ ያገኛሉ
- የኦዲትና ኢንስፔክሽን አገልግሎት ተጠሪነት ለቅዱስ ሲኖዶሱ ይኾናል
(አዲስ ጉዳይ፤ ቅጽ ፰ ቁጥር ፪፻፲፮፤ ግንቦት ፳፻፮ ዓ.ም.)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመጨረሻውና ከፍተኛው የሥልጣን ባለቤት ለኾነው ቅዱስ ሲኖዶስ÷ ቤተ ክርስቲያኒቱን የመጠበቅ፣ የመምራትና የማስተዳደር ዓላማዎቹን የሚያስፈጽምባቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ለማደራጀትና በተለያዩ የሞያ ዘርፎች በማማከር የሚያገለግል የመማክርት ጉባኤ ለማቋቋም በሚያስችል የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቅ ላይ በምልዓተ ጉባኤው ውይይት እየተካሔደ መኾኑን የአዲስ ጉዳይ ምንጮች ጠቆሙ፡፡
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 6 ቀን 2006 ዓ.ም. የተጀመረው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ኹለተኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ከሚነጋገርባቸው ኻያ ሦስት አጀንዳዎች መካከል ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶታል የተባለው የሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ማሻሻያ ረቂቁ በ99 ገጾች ካካተታቸው 80 አንቀጾች መካከል፣ ቅ/ሲኖዶሱ ዓላማዎቹን ስለሚያስፈጽምባቸው አካላት በሚዘረዝረው አንቀጽ 6 ንኡስ አንቀጽ 2(4) እና (5) ተጠሪነታቸው ለቅ/ሲኖዶስ የኾኑ መምሪያዎች(የሥራ ክፍሎች)፣ ቋሚ ኮሚቴዎች እንዲሁም ሊቃውንት፣ ካህናትና ምእመናን የሚገኙበት የመማክርት ጉባኤ እንደሚኖሩት ተመልክቷል፡፡
በሕግ ማሻሻያ ረቂቁ አንቀጽ 12(3) መሠረት፣ ከላይ ወደ ታች እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በተዘረጋው የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን መዋቅር ኹሉ ላይ የበላይ አካል ኾኖ ሕጎችን፣ ልዩ ልዩ ደንቦችንና መመሪያዎችን የማውጣት የዳኝነት ሥልጣን ላለው ለቅዱስ ሲኖዶሱ ተጠሪ ኾነው ይደራጃሉ የተባሉት ቋሚ ኮሚቴዎች ቁጥር ሰባት ሲኾን ዝርዝርቸውም፡-
- የእምነትና የትምህርት ጉዳዮች፣
- የቤተ ክርስቲያን ሕግጋት ጥናትና ዝግጅት፣
- የአህጉረ ስብከትና የገዳማት ጉዳዮች፣
- የውጭ ግንኙነት፣
- የልማትና ፕሮጀክት ጉዳዮች፣
- ኦዲትና ኢንስፔክሽን፣
- የሥነ ምግባርና የሥነ ሥርዓት ኮሚቴዎች
እንደኾኑ ተገልጧል፡፡
ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን እየተመለከቱ፣ እያጠኑና እየመረመሩ፣ የየመምሪያዎቹንና የአህጉረ ስብከትን የሥራ አፈጻጸም እየገመገሙ የውሳኔ ሐሳቦችን የሚያቀርቡ ተጨማሪ ኮሚቴዎች በቅ/ሲኖዶሱ ሊቋቋሙ እንደሚችሉ ያመለከተው ረቂቁ፣ የኮሚቴዎቹ አባላት ከቅ/ሲኖዶስ አባላት መካከል የሚመረጡና አስፈላጊ ኾኖ በተገኘ ጊዜ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ከምእመናንም ባለሞያዎች የኾኑ ምሁራን ተመርጠው በአማካሪነት አብረው እንደሚሠሩ አስታውቋል፡፡
በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ለማማከርና በየሞያ ዘርፉ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማገልገል ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ የኾነ አንድ የመማክርት ጉባኤ እንደሚቋቋም በማሻሻያ ረቂቁ ተጠቅሷል፡፡ የመማክርት ጉባኤው ተሳታፊዎች ከየሀገረ ስብከቱ የተመረጡ ‹‹ኦርቶዶክሳውያን ምሁራን›› እንደሚኾኑ በረቂቁ አንቀጽ 12(4) ሰፍሯል፤ ተሳታፊ ምሁራኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎታቸውና በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የሕዝበ ክርስቲያኑ ዕውቅና ያላቸው እንደሚኾኑ አመልክቷል፤ የመማክርት ጉባኤው ስብሰባዎች በዓመት ኹለት ጊዜ የሚደረጉና በፓትርያርኩ ሰብሳቢነት እንደሚካሔዱም ገልጧል፡፡
ቋሚ ኮሚቴዎቹና የመማክርት ጉባኤው በራሳቸው የሚዘጋጅ የውስጥ ደንብ ይኖራቸዋል፤ የሥራ አፈጻጸማቸውንም በየሩብ ዓመቱ ለቅዱስ ሲኖዶሱ ጽ/ቤት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
በሌላ በኩል የሊቃውንት ጉባኤ፣ መንፈሳዊ ፍርድ ቤት፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን አገልግሎት፣ የሥነ ሥርዓትና የሥነ ምግባር ዘርፍ የመሳሰሉት አካላት÷ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ዓቢይ ጉባኤ ቅ/ሲኖዶስ ተጠሪ የሚኾኑበትን አሠራር ለመዘርጋት መታሰቡን የሕግ ማሻሻያ ረቂቁ ጠቁሟል፡፡
በሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቁ በአዲስ መልክ የተካተቱት አካላት፣ ቋሚ ኮሚቴዎችና የመማክርት ጉባኤ የማቋቋም ሐሳብ የምልዓተ ጉባኤውን ስምምነት አግኝቶ ከጸደቀ፥ ፓትርያርኩ፣ ሊቃነ ጳጳሳቱና ኤጲስ ቆጶሳቱ በአባልነት የሚገኙበትን የቅ/ሲኖዶሱን የአመራር፣ የአስተዳደር፣ የቁጥጥርና የመወሰን ብቃት በማገዝ፣ አሠራሩን በማቀናጀትና በማጠናከር የጥንታዊቷን ቤተ ክርስቲያን ሥር የሰደደና የቆየ አስተዳደራዊ ችግር ሩቅ በማይባል ጊዜ ለመፍታትና ለውጦችን ለማየት እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡
ፓትርያርኩ በምልዓተ ጉባኤው ስብሰባ መክፈቻ ላይ በሰጡት መግለጫ የቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔዎች በጥናት ላይ ተመሥርተው ደረጃ በደረጃ በተግባር ለመተርጎምና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልናና ክብር፣ አንድነትና ሥርዓት እንደነበረው አጠናክሮ ለመቀጠል የሚያስችሉ ውሳኔዎች በቅ/ሲኖዶሱ እንደተወሰኑ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
Good bless You for all your effort
Amasaginalawu
ምንት ረባሁ ለመሰንቆ ጽሩእ ለእመ አልቦ ዘይሰነቅዎ
ይህ ነገር የረጅም ጊዜ ቤተክርስቲያንን የመቆጣጠሪያ እቅድ ይሆን ብዬ አሰብኩና ሆዴን ባር ባር አለው። ከዚህ ቀደም የትኛው ሕግ በተግባር ሲተረጎም አየን? ታዲያ ይህ ጥሩ የሚመስል እቅድ የመንግስት የረጅም ጊዜ እቅድ ከኋላው እንደሌለ በምን እርግጠኞች እንሆናለን?
እንደው ማኅበረ ቅዱሳን ሰራው ቢሉኝ ኖሮ ለቤተ ክርስቲያን ታስቦ የተሰራ ነው እል ነበር። ደግሞም ተቃውሞ ይበዛበት ነበር።
አሁን ግን ሁኔታው አስፈራኝ።
ብቻ አባቶቻችንን የመከፋፈል፣ የፓትርያርኩን ቦታ የማዳከም ሥራ እንዳይሆን።
እግዚአብሔር ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን።
ተዋሕዶ የልቤን አውጥተህ ስለጻፍክልኝ አመሰግናለሁ። ይህንን እና ለፓትርያሪኩ እንደራሴ የመሾሙን ነገር ሳስበው በምስጢር የተቀነባበረ ነገር ያለ ነው የሚመስለኝ። በኔ አስተያየት ሁለቱም አስፈላጊ አደሉም። ምናልባት ቅዱስ ሲኖዶስ በቋሚ ኮሚቴዎች እና በመማክርት ጉባኤ ቢደራጅ መጠነኛ የሆነ ጥቅም ሊኖረው ይችላል፤ ነገር ግን ስንት አንገብጋቢ ጉዳይ እያለ በነዚህ ሁለት ጉዳዮች ላይ ትኩረት መሰጠቱን ሳስበው ለሴራ የተቀነባበረ ይመስለኛል። ለመሆኑ ፓትርያሪኩ ምኑን ሰርተውት ነው ሥራው የበዛባቸው። ዋናው ሥራ መሰራት የነበረበት እኮ ባንድ ሰው ብቻ ሳይሆን በቤተ ክህነቱ መዋቅር ነው። ስለዚህ ቤተ ክህነቱን ማጽዳት ሲያስፈልግ፥ የሌለ ችግር አለ ብሎ መፍትሄ ለመፈለግ መጣር ድካም ብቻ ነው ትርፉ። እስቲ የሌሎች አብያተ ክርስቲያናት እንደዚህ ዓይነት የእደራሴ ባህል ካላቸው ብትገልጹልን መልካም ነው። እኔ ግን ምንም መልካምነቱ አይታየኝም። በቢልዮን የሚቆጠሩ ምእመን ያላት የካቶሊክ ቤ/ን እንደራሴ ፓትርያሪክ ከሌላት ለኛ የሚያስፈልግበት ሁኔታ አይታየኝም። This is just my suspicion and I may be wrong.
ቅዱስ ሲኖዶሱ በቋሚ ኮሚቴዎች እና በመማክርት ጉባኤ ሊደራጅ ነው ለፓትርያርኩ እንደራሴ እንደሚመደብ የሚገልጽ የሕግ ረቂቅ ለውይይት ቀረበ ስለዚህ ወደፊት ፓትርያርኩ ቋሚ ኮሚቴዎችን ሲመሩ፣ እንደራሴው ደግሞ የመማክርት ጉባኤውን ይመራሉ። አለመስማማት ቢፈጠር የአገሪቱን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል መንግስት ።።። እርምጃ ይወስዳል።